#COVID19 የዩናይትድ ስቴትስ ፕሬዚደንት ዶናልድ ትረምፕ የኮሮናቫይረስ ስርጭትን ለመዋጋት የሚውል ስምንት ነጥብ ሶስት ቢሊዮን ዶላር አስቸኳይ ወጪ የመደበውን ህግ ትላንት በዋይት ሃውስ ፈርመዋል። ኮሮናቫይረስ ከዋሽንግተን አቅራቢያ ሚሪላንድ ክፍለ ግዛት ውስጥ ወደሚገኝ አውራጃ ተዛምቷል። የተመደበው ገንዘብ በቫይረሱ ለተጋለጡ ህክምና እና የመከላከያ ክትባት ፍለጋ ለክፍለ ግዛቶች እና የአካባቢ አስተዳደሮች ዕርዳታ የሚውል መሆኑ ተጠቁሟል። በጀቱ የተፈቀደበትን ህግ የዩናይትድ ስቴትስ የመወሰኛው እና የተወካዮች ምክር ቤቶች ትናንት በሙሉ ድምጽ በሚባል ደረጃ አጽድቀውታል። #VOA

COVID19

ከዋይት ሃውስ ጥቂት ደቂቃዎች ርቀት ላይ ምትገኘው የሚሪላንድ ሞንትጎመሪ ካውንቲ ውስጥ የመጀመሪያ በቫይረሱ [COVID-19] መጋለጣቸው የተረጋገጠ ሰዎች በመገኘታቸው የክፍለ ግዛትዋ ሀገረ ገዢ ሌሪ ሆጋን አስቸኳይ ጊዜ አውጀዋል።

VOA

ኮንትራት ሶስት!

በሞጆ – ሀዋሳ የፍጥነት መንገድ ግንባታ ከባቱ እስከ አርሲ ነጌሌ (የኮንትራት ሶሰት) የግንባታ ሂደት መጓተቱ ተገልጿል።

የመንገዱ ግንባታ ሂደት አሁን ላይ መድረስ ከነበረበት 37 በመቶ አፈፃፀሙ 6 ነጥብ 8 በመቶ ብቻ መሆኑም ታውቋል።

የፕሮጀክቱ ምክትል አማካሪ የሆኑት ኢንጂነር ካሳሁን ጣሰው የመንገዱ ግንባታ የተጓተተው በግንባታ ግብዓት ፍቃድ ችግር፣ በወሰን ማስከበርና በወረዳ አስተዳደር ትብብር ማነስ መሆኑን ተናግረዋል።

ለግንባታው ግብዓት ለማግኘት ብቻ ከአንድ ዓመት በላይ እንደወሰደም ኢንጂነር ካሳሁን ገልጸዋል። ለመንገዱ ግንባታ የነበረውን አመለካከት ለመቀየር ከወረዳ አመራሮች ጋር ውይይት በማድረግ መፍትሄ መምጣቱንም ተናግረዋል።

ኢዜአ

የሶስት ሰው ህይወት ጠፍቷል!

ቦሌ ሞርኒንግ ስታር ሞል በሚገኘው ‘እናት ባንክ’ የሚሰሩ ጥበቃዎች መካከል በተፈጠረው ግጭት የ3 ሰው ህይወት ማለፉን የቲክቫህ ቤተሰቦች ገልፀዋል። ፖሊስ የማጣራት ስራ እየሰራ ይገኛል፤ በአካባቢው አምቡላንስ እየተመላለሰም እንደሆነ የቤተሰባችን አባላት አሳውቀዋል።

@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia

Published by Habesha Herald

We get you up to date News from every corner of the world .

Leave a comment

Design a site like this with WordPress.com
Get started