በኢትዮጵያ እስካሁን በኮሮና ቫይረስ የተጠቃ ሰው…🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹

COVID19

በኢትዮጵያ እስካሁን በኮሮና ቫይረስ የተጠቃ ሰው ባይኖርም በሽታውን ለመከላከል ማኅበረሰቡ የግል ንጽሕናውን በአግባቡ በመጠበቅ የራሱን ቅድመ ጥንቃቄ ማድረግ እንደሚገባው የኢትዮጵያ ሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት አስታውቋል።

በሽታው ወደ ሀገር ቢገባ ከሚደረጉ ቅድመ ጥንቃቄዎች መካከል የተለያዩ ማእከላትን ግብዓት በማሟላት አስፈላጊ ዝግጅቶች እየተደረጉ መሆኑንም የኢትዮጵያ ሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር ዶክተር ኤባ አባተ ተናግረዋል።

በአሁን ሰዓት የቫይረሱ ምልክት ታይቶባቸው በማቆያ ማእከላት ውስጥ አምስት ግለሰቦች የሚገኙ ሲሆን፣ ከዚህ ቀደም በማእከሉ ክትትል ሲደረግባቸው የነበሩ ከ900 በላይ ሰዎች ክትትላቸውን ጨርሰው መውጣታቸውንም ዋና ዳይሬክተሩ አስታውቀዋል።

ኢቢሲ #የህብረተሰብጤናኢንስቲትዩት

Published by Habesha Herald

We get you up to date News from every corner of the world .

Leave a comment

Design a site like this with WordPress.com
Get started