
የ20/80 ኮንዶሚኒየም ቤቶች ለዕድለኞች ሊተላለፉ ነው!
የተገነቡት “በኦሮሚያ ክልል ላይ ነው” በሚል ውዝግብ ተቀስቅሶባቸው ከነበሩ የአዲስ አበባ ኮንዶሚኒየም ቤቶች ውስጥ ሰላሳ ሁለት ሺህው ከሚቀጥለው ሳምንት ጀምሮ ዕጣ ለወጣላቸው ዕድለኞች ሊተላለፉ እንደሆነ ሪፖርተር ዘግቧል።
እንደ ሪፖርተር ዘገባ ከሆነ የኮንዲሚኒየም ቤቶቹን ውዝግብ እንዲያጠና ከአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር እና ከኦሮሚያ ክልል ተውጣጥቶ የተቋቋመው ኮሚቴ፤ ዕጣ ከወጣባቸው የጋራ መኖሪያ ቤቶች ውስጥ 9,000 ያህሉ በኦሮሚያ ክልል ውስጥ መገንባታቸውን አረጋግጧል።
ምንጭ፦ ሪፖርተር ጋዜጣ