
PASSPORT
የINVEA 10 ሰራተኞች በቁጥጥር ስር ውለዋል!
በአስቸኳይ ፓስፖርት ለማውጣት የሚጠየቁ መስፈርቶችን ያላሟሉ እና መደበኛውን ፓስፖርት ያለአግባብ ሲሰጡ የነበሩ ሰራተኞች እንደነበሩ በዛሬው ዕለት ተገልጿል።
ያለአግባብ መስፈርቱን ላላሟሉ እና ለውጭ ዜጎች ፓስፖርት የሰጡ 10 ሰራተኞች በቁጥጥር ስር መዋላቸው ተነግሯል። በተደረገው የማጣራት ስራ ሰራተኞቹ ከውጭ ዜጎቹ ከ5 ሺህ ዶላር በላይ መቀበላቸውን ተገልጿል፤ 77 የሚሆኑ ፓስፖርቶች በህገ ወጥ መልኩ ተሰርተው መገኘታቸውንም ተሰምቷል።
ከዚህ ጋር ተያይዞም ፓስፖርቶቹ ጥቅም ላይ እንዳይውሉ ለኢንተርፖል ማሳወቅ እና ሰዎቹን ተጠያቂ የማድረግ ስራ መስራቱ የፌደራል ኢሚግሬሽን ዜግነትና ወሳኝ ኩነት ኤጀንሲ ገልጿል።