
የማስክ ጉዳይን በሚመለከት፦
- ይሄ በሽታ ተከሰተ ማለት ሁሉም ማስክ ያድርግ ማለት አይደለም።
- አሁን ባለው ሁኔታ ማስክ ማደረግ የሚጠበቅባቸው ሰዎች ዋነኛዎቹ በኮሮና ቫይረስ በሽታ የተያዙ ፣ የጉንፋን መሰል ምልክቶች የሚታይባቸው ፣ የማሳል ፣ ትኩሳት ያለባቸው ሰዎች ወደሌላ እንዳያስተላልፉ ማስክ እንዲያደርጉ ያስፈልጋል።
- በኮሮና ቫይረስ ለሚጠረጠሩ ሰዎች የህክምና ድጋፍ እና ክትትል የሚያደርጉ የጤና ባለሞያዎችም ማስክ መጠቀም አለባቸው።