
COVID19
ትላንት ጎረቤታችን ሱዳን ውስጥ አንድ ግለሰብ ህይወቱ አልፏል ፤ ይህ ግለሰብ በኮሮና ቫይረስ ተይዞ እንደነበረ ሀገሪቱ አስታውቃለች፡፡
ህይወቱ ያለፈው ግለሰብ በዚህ ወር የተባበሩት አረብ ኢሚሬትስን ጎብኝቶ እንደነበረ ነበረና ሀሙስ እለት ህይወቱ ማለፉ ነው የታወቀው፡፡
በ50ዎቹ ዕድሜ ውስጥ የነበረው ግለሰብ በሱዳን ዋና ከተማ ካርቱም ውስጥ መሞቱን የአገሪቱ የጤና ጥበቃ ሚኒስትር በሰጠው መግለጫ አስታውቋል፡፡