
UPDATE
የኮሮና ቫይረስ በአዲስ አበባ መከሰቱን ተከትሎ ያልተገባ የዋጋ ጭማሪ የሚያደርጉ ነጋዴዎችን የሚቆጣጠር ግብረሀይል ተቋቁሟል ተባለ።
በከተማዋ የንግድ ቢሮ የሚመራው ግብረሀይሉ ከነገ ጠዋት ጀምሮ ወደ ስራ ይገባል ተብሏል። ባልተገባ መልኩ የዋጋ ጭማሪ የሚያደርጉ ነጋዴዎች ላይ ህጋዊ እርምጃ የሚወሰድ መሆኑንም ነው የከተማ አስተዳደሩ ያስታወቀው።
ህብረተሰቡ ካልተገባ የዋጋ ጭማሪ እራሱን እንዲጠብቅና በዚህ አይነት መልኩ የዋጋ ጭማሪ የሚያደርጉ ነጋዴዎችን በተመለከተ ጥቆማ እንዲሰጥ የከተማ አስተዳደሩ አሳስቧል።
ምንጭ፦ etv