
COVID19
የካናዳው ጠቅላይ ሚኒስትር ጀስቲን ትሩዶ ባለቤት ሶፊ ግሪጎሪ በኮሮና ቫይረስ መጠቃታቸው መረጋገጡን ቢቢሲ ዘግቧል።
ሶፊ ግሪጎሪ ዩናይትድ ኪንግደም ውስጥ ንግግር አድርገው ከተመለሱ በኋላ የተወሰነ የሕመም ምልክት ማሳየታቸውን ተከትሎ በተደረገ ምርመራ ነው በቫይረሱ መያዛቸው የተረጋገጠው።
በዚህም ጠቅላይ ሚኒስትሩ በቫይረሱ ስጋት ምክንያት ለ14 ቀናት ብቻቸውን ለመቆየት መወሰናቸውን የጠቅላይ ሚኒስትሩ ጽ/ቤት አስታውቋል።
ጠቅላይ ሚኒስትሩ የጤናቸውን ሁኔታ በከፍተኛ ጥንቃቄ እየተከታተሉ የዕለት ተዕለት ሥራቸውን ቤታቸው ሆነው እንደሚሠሩ ጽ/ቤቱ በመግለጫው አመልክቷል።