
EthiopianAirlines
http://www.fidelpost.com (ፊደል ፖስት) የተሰኘው የመረጃ ማሰራጫ ከታማኝ ምንጮች ነው መረጃውን ያገኘሁት ብሎ እንደዘገበው ከነገ መጋቢት 9/ 2012 ዓ/ም ጀምሮ በኮሮና ቫይረስ [COVID-19] ስርጭት ስጋት ምክንያት የኢትዮጵያ አየር መንገድ በረራዎቹን ሰርዟል።
አየር መንገዱ ወደ ሱዳን [ካርቱም]፣ ግብፅ [ካይሮ]፣ ሊባኖስ [ቤሩት]፣ ፈረንሳይ [ፓሪስ] ፣ ኬንያ [ናይሮቢ እና ሞምባሳ] እንዲሁም ኳታር [ዶሀ] የሚያደርገውን በረራ ነው ላልተወሰነ ጊዜ የሰረዘው። የዱባይ እና የሌሎች ሀገራትንም በረራ ሊሰርዝ ይችላል ሲልም ድረገፁ አስነብቧል።