

..”መልካም ተግባር
የባልደራስ ፕሬዝደንት እስክንድር ነጋ ሰሞኑን የመሰረት ድንጋይ በተጣለበት መገናኛ 24/ አርሴማ ቤተክርስቲያን በመገኘት በግላቸው የ1ሺህ ብር ድጋፍ አደርገዋል። አቶ እስክንድር ነጋ ጨምሮ አቶ ስንታየሁ ቸኮል ለቤተክርስቲያኗ መልሶ ግንባታ የጉልበት ስራ በመስራት ያገለገሉ ሲሆን በነዋሪዉ በተደረገላቸው ጥሪ ቦታው ላይ በመገኘት በቻሉት ሁሉ የድጋፍ እርዳታ ማበርከታቸው ያካባቢውን ወጣት እንዳስደሰተ ገልጸዋል።
በሌላ በኩል ያዕቆብ ዳንኤል የተባለ የአዲስ አበባ ወጣት መገናኛ 24/ አርሴማ ቤተክርስቲያን አጠገብ የሚኖር በወቅቱ ቤተክርስቲያኗ አትፈርስም በማለት በኦሮሚያ ልዩ ሃይል ቶክስ በጥይት ከተመቱ ሰዎች መሀል አንዱ ነበር። ወጣት ያዕቆብ ዳንኤል ጉልበቱን ከተመታ ጀምሮ ከፍተኛ እንግልት እና ስቃይ ማሳለፉ የሚታወቅ ነው።
ዛሬ የባልደራስ አመራር ወደ አርሴማ ጎራ ባሉበት አጋጣሚ በሰፈር ሰዎች ጥቆማ ወደ ያዕቆብ ዳንኤል መኖሪያ ቤት በመሄድ ወጣቱን በመጎብኘት ጠይቀዋል። ወጣት ያዕቆብ ዳንኤል በጸጥታ ሃይል የደረሰበት አስነዋሪ ድርጊት ከአንደበቱ ሲናገር ለመታዘብ ተችሏል። ሙሉዉን ዝርዝር ከመረጃ ቲቪ ይከታተሉ። ይህን ወጣት በህክምና ለማገዝ የምትፈልጉ ሰዎች በውስጥ መስመር አድራሻውን መስጠት ይቻላል።
ምንጭ ስንታየው ቸኮል