
የኮሮና ቫይረስ አለምን እያመሳት ነው። በቫይርሱ የሚያዙ እና የሚሞቱት ሰዎች ቁጥር በየቀኑ እየጨመረ ነው። በሀገራችን እስካሁን የታወቁ ኬዞች 6 ናቸው። ቫይርሱን ለመግታት እስካሁን በምንግስት እና ህዝብ እየተደረገ ያለው ርብርብ ጥሩ ነው፡: ሁለት ነገሮች ላይ መንግስት እና ህዝብ ውሳኔ መስጠት የሚያስፈልግ ይመስለኛል።
1) በሀገራችን ህዝቡ በገራ በዛ ብሎ ፈጣሪውን እንደሚያመልክ ይታወቃል። ይህ ደግሞ ለቫይረሱ ተጋላጭነትን ይጨምራል። ስለዚህ የሀይማኖት አባቶች ስለ ጁምዓ እና የሰንበት ጸሎቶች ወስነው ምዕመናኑን ማሳወቅ አለባቸው።
2) ሳምንታዊ ገበያዎች ህዝባችን ከገጠር በሺዎች ተምሞ የሚገበያይበት ነው። ይህ ደግሞ ቫይረሱ በቀላሉ እንዲስፋፋ እና ወደገጠር እንዲገባ እድል ይሰጠዋል። ስለዝህ መንግስት በገበያ ጉዳይ ላይ አፋጣኝ ወሳኔ አሳልፎ ለህዝቡ ማሳወቅ አለበት።