ትናንት በጎንደር ከተማ እና አካባቢዋ በተኩስ ልውውጥ የታጀቡ በርካታ ግጭቶች የተስተዋሉ ሲሆን፣ በሰዎች ላይ የሞትና የአካል ጉዳት ደርሷል። ግጭቶች የተቀሰቀሱት መንግስት ፋኖ ተብሎ በሚጠራው ቡድን ላይ ጥቃት ከፍቷል መባሉን ተከትሎ ነው።
- ትናንት ከሰዐት የጸጥታ ሀይሎች መንገድ በዘጉ ወጣቶች ላይ ተኩስ ከፍተው 3 ሰዎች አቁስለዋል።
- ምሽት 12 ሰዐት ከአዘዞ ካምፕ ወደ ጎንደር ከተማ በመግባት ላይ በነበሩ የመከላከያ ሰራዊት አባላት ላይ ያልታወቁ ሰዎች ተኩስ ከፍተው ጉዳት አድርሰዋል